19 Mar 2026, 18:02 UTC88 views3 reactionsread 9 August 2026 መዝሙር 129
አቤቱ አንተን ከጥልቅ ጠራሁህ:አቤቱ ድምፄን ስማ።
ጆሮህ የልመናዬን ቃል የሚያደምጥ ይሁን:አቤቱ ሃጢያትንስ ብትጠባበቅ
አቤቱ ማን ይቆማል?
ስለ ስምህ ይቅርታ ከአንተ ዘንድ ነውና
አቤቱ ተስፋ አደረግኩህ: ነፍሴ በሕግህ ታገሠች።
ከጧት እስከ ሌሊት።
ነፍሴ በእግዚአብሔር ታመነች።
ከእግዚአብሔር ዘንድ ምሕረት ።
በእርሱም ዘንድ ብዙ ማዳን ነውና
ከጧት ጀምሮ እስራኤል በእግዚአብሔር ይታመን።እርሱም እስራኤልን ከሃጢአቱ ሁሉ ያድነዋል።
አቤቱ ልቤ አይታበይብኝ😢
አይኖቼም ከፍ ከፍ አይበሉብኝ
ከትልልቆች ጋር ከእኔም ይበልጥ ከሚከበሩ ጋር አልሄድኩም
ነፍሴን አሳረፍኳት
የእናቱንም ጡት እንዳስተውት ዝም አሰኘኋት ።ነፍሴ የእናቱን ጡት እንዳስተውት በእኔ ው…
🥰2❤1
13 Mar 2026, 14:23 UTC107 views3 reactionsread 9 August 2026 ስላለፍንባቸውስ ትላንትናዎች ምናልባት ወደፊቶችም ትንሽ እንበል እስኪ✍️
🏵በነገራችን ላይ በሕይወት ካለን በመኖር ውስጥ መሰበር የሚባል ህመም አለ።አንዳንድ ስብራቶች ደግሞ ልባችን ከቦታዋ የለቀቀች ያህል እንዲሰማን ያደርጋሉ።ሆኖም የፈጣሪን ጠብቆትና ምሕረት እስኪያስረሱን ግን መሆን የለበትም።ዓለም🌍 ላይ እኛ ላይ ብቻ የሃዘን ድንጋይ ለመወርወር ያመቻቹን እስኪመስለን ድረስ ይሰማናል።አላፊ አግዳሚው ሁሉ የሚዘባበትብንና እኛን ሆን ብሎ ለማቁሰል የሚረማመድብን መስሎ የሚሰማን ጊዜም ይኖራል።
ሕይወት ቀላል አይደለችም😣በቀላሉ የምታሸንፈው ጦርነት እንደሌላት አርገህ እንድታስብ ታስገድድሃለች!
በእርግጥ ሁሉም ሰው ሊያሸንፈው የተፈቀደለት ቢያንስ አንድ ትግል አለው።…
👍3
12 Mar 2026, 07:54 UTC99 views4 reactionsread 9 August 2026 Photo
Photo, posted without a caption
🥰4
9 Mar 2026, 10:56 UTC120 views4 reactionsread 9 August 2026 Photo
ይህ አካሌ:በክፉ በሽታ:እድሜውን ቢቀጣም፣
ከንፈር መጣጭ ወዳጅ:እርሱ እኮ ተረስቷል:የሚለኝ ባላጣም፣
እውነት እልሃለሁ😢
ልትድን ትወዳለህ:ብሎ የጠየቀኝ:ካላንተ ጎጆዬ:መድኃኒት አልመጣም።
ምን አለኝና:የሚነገር ታሪክ:በደዌ በሽታ:ከመማቀቅ በቀር፣
ስሜን መፃጉዕ አሉት:መራመድ ማያውቀው:እግሬ ከቤት ቢቀር።
ልታሽለኝ መጣህ:ልታነፃኝ ወደድህ:አዘነበልክልኝ:በሰንበት ሞሸርከኝ፣
የተሸከመኝን አልጋዬን አዝዬ:በሰዎች መካከል:ቀና እንድል አረከኝ።
አያልቅብህ ምሕረት:አትጎድልም ፀጋህ:አትሰስትምና:ፈውስን ትሰጣለህ፣
በሰው የተተወን:አታረፍድምና:በጊዜህ በቦታህ:ድንቅን ታደርጋለህ።
ከማይነጥፍ እጅህ:በረከትህ ተርፎኝ:ሃጢአት እንዳላደርግ:ቃልህ ቢገዛኝም፣
ከአይሁዶች ሸንጎ ልተ…
🥰3❤1
7 Mar 2026, 06:59 UTC107 views6 reactionsread 9 August 2026 አንዴ ለራሳችን ደጋግመን እድል እንስጥ
ከሃሳቤ ክታብ ሰርቄ ከጻፍኳት✍️
በነገራችን ላይ ለራስ ደጋግሞ እድል እንደመስጠት መልካም ነገር የለም።ለመሻሻል ለማደግ ወደፊት እግርን ለማስቀጠል እና ራስን ለመጠበቅ ምርጡ ነገር ለራስ ሳይሰስቱ ደጋግሞ እድል መስጠት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው።
ለሰዎች ስንት ጊዜ ሕይወታችን ውስጥ እንዲደጋገሙ እድል ሰጥተናቸው ይሆን?
ለኛስ ደጋግመን እንድንበረታ እና ለራሳችን ለመሆን እድል የምንሰጠው መቼ ነው?
ከራሳችን አልፈን ለሰዎች መድረስ አላማችን ከሆነ ሳንሰለች ለራሳችን የማያልቅ አንድ እድል ያስፈልገናል!!
✍️ግእዛዊት
🔥6
ግእዛዊት✍️ pinned «መቼ ነው የቆሸሸ ቤተ መቅደሴን ልታጸዳው የምትመጣው😥 ዛሬ ለሊት እንቅልፍ ባጣም እግረ መንገዴን እራሴን ላለማጣት በፍርሃት ከጻፍኳት✍️ እንደሚታወቀው ይህ ሳምንት የአብይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት ምኩራብ የሚል ስያሜም እንዳለው እሙን ነው።እኔ ግን ይህን ሳምንት ሳስበው ጌታችን ልክ እንዳደረገው ወደ ኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ ሄዶ ከመቅደሱ በደረሰ ጊዜ ቤተ መቅደሱን ባልተገባ ሁኔታ የንግድ ቦታ ሆኖ ነበር…»
5 Mar 2026, 13:13 UTC124 views5 reactionsread 9 August 2026 መቼ ነው የቆሸሸ ቤተ መቅደሴን ልታጸዳው የምትመጣው😥
ዛሬ ለሊት እንቅልፍ ባጣም እግረ መንገዴን እራሴን ላለማጣት በፍርሃት ከጻፍኳት✍️
እንደሚታወቀው ይህ ሳምንት የአብይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት ምኩራብ የሚል ስያሜም እንዳለው እሙን ነው።እኔ ግን ይህን ሳምንት ሳስበው ጌታችን ልክ እንዳደረገው ወደ ኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ ሄዶ ከመቅደሱ በደረሰ ጊዜ ቤተ መቅደሱን ባልተገባ ሁኔታ የንግድ ቦታ ሆኖ ነበር የጠበቀው።ጊዜውም ስለደረሰ እንደ ቀድሞው ቤተ መቅደስ ገብቶ ተምሮ እና ጠይቆ እንዲሁም አስተምሮ ብቻ መውጣትን አልወደደም ነበር።
ይልቁንም የቤተ መቅደሱን ደጅ የንግድ ቦታ ስላደረጉት ገንዘብ ወዳዶችን እንስሳትን በገንዘብ ሲሸጡ እና ሲለውጡ በዝምታ ሊያልፋቸው …
👏3👍2
4 Mar 2026, 16:39 UTC280 views2 reactionsread 9 August 2026 Photo
ካለወትሮው...
ከማጀቴ እርሜን ባጣ: ጤዛ ሆኖ በረከቴ: ድንገት ከእጄ ወጥቶ ቢርቅ፣
አላወርድም ዘለላ እንባ:አልደቃውም ይህ ደረቴን: አልገኝም ስነፈርቅ::
ተትረፍርፎኝ ስለማውቀው:ስላይደለሁ የምሰፈር:በጠላቴ ድርድር ልክ፣
ምን ቢደላኝ ያልፋል ብዬ:ምን ቢተርፈኝ ቸርከኝ እያልኩ:ለስምህ ነው ምንበረከክ።
ከሲሳይህ አትርፌያለሁ:ፈትነው እንዳሻህ:የእምነቴን አጥር፣
እኔም በተራዬ:ኢዮብን አታይም:እያልኩ እፅናናለሁ:ለራሴ ትዕቢቴን:ላሸንፈው ስጥር።
እያልኩ ስልህ ኖሬ:ቃል ሳዘምት ከርሜ😢
አትይብኝ ስንገዳገድ:ምሉዕ አይደለም ቶማስ ልቤ:ባወራው ልክ አትመዝነው፣
ባይሆን ባይሆን😔
የዘመኔን ቁጥር ሰፍረህ:ሲጸናብኝ እንዳልክድህ :እድሜዬን ቀንሰው
ዛሬን እያየኸኝ...
ኪዳ…
❤2
ግእዛዊት✍️ pinned «መልካም ምግባራችሁን ጠብቁት!! በፍጥነት በመንገድ እየሄድኩ ከጻፍኳት እነሆ✍️✍️ በእኛ ሕይወት ውስጥ ብዙ አይነት የተለያየ ስብዕና ያላቸው ሰዎች አሉ እኮ! አይደል?ፈቅደንላቸውም ሆነ ሳንፈቅድላቸው ወደ እኛ ሕይወት በአጋጣሚሚም ሆነ በምክንያት የሚገቡ።እነኚህ ሰዎች ናቸው እንግዲህ አካባቢያችን እንዲሆኑ ከፈቀድንላቸው በኋላ በማንነታችን ላይ አሻራ የሚጥሉት እና በአመለካከታችን ላይ ለውጥ የማምጣት…»
4 Mar 2026, 13:08 UTC136 views3 reactionsread 9 August 2026 መልካም ምግባራችሁን ጠብቁት!!
በፍጥነት በመንገድ እየሄድኩ ከጻፍኳት እነሆ✍️✍️
በእኛ ሕይወት ውስጥ ብዙ አይነት የተለያየ ስብዕና ያላቸው ሰዎች አሉ እኮ! አይደል?ፈቅደንላቸውም ሆነ ሳንፈቅድላቸው ወደ እኛ ሕይወት በአጋጣሚሚም ሆነ በምክንያት የሚገቡ።እነኚህ ሰዎች ናቸው እንግዲህ አካባቢያችን እንዲሆኑ ከፈቀድንላቸው በኋላ በማንነታችን ላይ አሻራ የሚጥሉት እና በአመለካከታችን ላይ ለውጥ የማምጣት ብቃት የሚኖራቸው።መልካም ከሆኑ እሰየው እንምሰላቸው😊ችግሩ እሱ አይደለም😊ለእነርሱ እንኳ ማረም የከበዳቸውን አልያም አልላቀቅ ያላቸውን እኩይ አመላቸውን ወደ እኛ እንዳይዘሩት እንጂ!
ሰዎች ጥሩ የተባለ ማንነታችሁን ሳትፈልጉ እንድትለውጡት እና መልካምነታችሁ ምን…
🔥2👍1
Channel photo updated
Channel created
Showing the 12 most recent of 12 posts we hold for @giizawit. View and reaction counts are the latest single reading for each post, not a live figure, and a recent post is still accumulating both. A view count marked ≈ was rounded by Telegram before we ever saw it — t.me prints views in full below 1,000 and to three significant figures above, so ≈1,200,000 means somewhere between 1,150,000 and 1,249,999. Unmarked counts are exact. Text is reproduced from the public post preview and truncated for length.