6 Sept 2024, 17:55 UTC≈4,020 views3 reactionsread 8 August 2026 እግዚአብሔር ሆይ ምሕረት አድርግልኝ
እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ ቸርነትህ መጠን፣ ምሕረት አድርግልኝ፤ እንደ ርኅራኄህም ብዛት፣ መተላለፌን ደምስስ (መዝሙር 51፥1)።
ዘማሪው በዚህ ቦታ እየደጋገመ “እንደ ቸርነትህ መጠን” እና “እንደ ርኅራኄህም ብዛት” “ምሕረት አድርግልኝ” ይላል።
በዘጸአት 34፥6-7 ላይ እግዚአብሔር ተስፋ የሰጠው ይህንን ነው፦
“እግዚአብሔር ሩኅሩኅ ቸር አምላክ እግዚአብሔር ለቍጣ የዘገየ፣ ፍቅሩና ታማኝነቱ የበዛ፣ ፍቅርን ለሺዎች የሚጠብቅ፣ ክፋትን፣ ዐመፅንና ኀጢአትን ይቅር የሚል በደለኛውን ግን ሳይቀጣ ዝም ብሎ አይተውም፤ በአባቶች ኀጢአት ልጆችን የልጅ ልጆቻቸውን እስከ ሦስትና አራት ትውልድ ይቀጣል።”
ይቅር የማይባሉ በደለኞች …
👍3
Signed Gech
3 Jun 2024, 04:02 UTC≈2,770 views1 reactionsread 8 August 2026 እግዚአብሔርን መውደድ ማለት ምን ማለት ነው?
እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ አምላኬ ነህ፤ አንተን ከልብ እሻለሁ፤ ውሃ በሌለበት፣ በደረቅና በተራቈተ ምድር፣ ነፍሴ አንተን ተጠማች፤ ሥጋዬም አንተን ናፈቀች። ስለዚህ በመቅደስ ውስጥ አየሁህ፤ ኀይልህንና ክብርህንም ተመለከትሁ። (መዝሙር 63፥1-2)
እንደ ዳዊት ያለውን ልብ ሊያረካ የሚችለው እግዚአብሔር ብቻ ነው። ዳዊት እንደ እግዚአብሔር ልብ የሆነ ሰው ነበር። የተፈጠርነው እንዲያ እንድንሆን ነበር።
እግዚአብሔርን መውደድ ማለት በዋነኛነት በእርሱ መርካት ማለት ነው። በስጦታዎቹ ብቻ ሳይሆን፣ በእግዚአብሔር በራሱ — ማለትም በከበረው ማንነቱ — መርካት ማለት ነው።
እግዚአብሔርን መውደድ ትዕዛዛቱን ሁሉ መታዘዝን…
❤1
Signed Gech
1 Jun 2024, 14:18 UTC≈2,100 viewsread 8 August 2026 ዳግም የተወለደ በሕጉ ደስ ይለዋል
እግዚአብሔርን መውደድ ትእዛዞቹን መፈጸም ነውና። ትእዛዞቹም ከባድ አይደሉም፤ ምክንያቱም ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ዓለምን ያሸንፋል። ዓለምን የሚያሸንፈውም እምነታችን ነው። ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ከሚያምን በስተቀር ዓለምን የሚያሸንፍ ማነው? (1ኛ ዮሐንስ 5፥3-5)
በዚህ ክፍል ላይ ግልፅ ሆኖ የምንመለከተው ነገር፣ ከእግዚአብሔር ዳግም መወለድ የእግዚአብሔርን ትዕዛዛት እንደሸክም ከመመልከት ይልቅ ደስ እንድንሰኝባቸው እንደሚያደርገን ነው። ታዲያ ግን ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል?
እንዴት ነው ከእግዚአብሔር መወለድ የእርሱን ትእዛዛት ሸክም ከመሆን ይልቅ ወደ ደስታ የሚቀይረው?
ሐዋሪያው ዮሐንስ ሲናገር፣…
Signed Gech
29 May 2024, 05:32 UTC332 viewsread 8 August 2026 File
፩. በደሙ አንጽቶሽ በቃሉ ቀድሶሽ
አሸናፊው ጌታ በሞቱ የገዛሽ
ክብርትና ቅድስት ያለ ነውርም ኾነሽ
የሙሽራሽን ቀን ለማየት የናፈቅሽ
አዝማች፤
ደስ ይበልሽ አንቺ ቅድስት ቤተክርስቲያን
የጠላትን ግፊያ ችለሽ ብዙ ዘመን
ታምነሽ ቆይተሻል እንደ ቃል ኪዳንሽ
ቀኑ በደጅ ነው ያ አስደናቂው ሰርግሽ
፪. ሙሽራሽ የዋህ ነው ተንኰል የሌለበት
ፍጹምና ታማኝ ጉድለት ያልታየበት
ሙሽራሽ ኢየሱስ የሰላም አለቃ
አንዳችም የማይጎድለው ለሁሉ የሚበቃ
አዝማች፤
ደስ ይበልሽ አንቺ ቅድስት ቤተክርስቲያን
የጠላትን ግፊያ ችለሽ ብዙ ዘመን
ታምነሽ ቆይተሻል እንደ ቃል ኪዳንሽ
ቀኑ በደጅ ነው ያ አስደናቂው ሰርግሽ
፫. የሐሰት ተቃራኒ የእውነት አምድ ነሽ
በእሳት የነጠሩ ጻድቃን የሞ…
Signed Gech
16 May 2024, 07:28 UTC≈1,550 viewsread 8 August 2026 ትክክለኛ እውቀት ታላቅ ደስታን ያመጣል
ስለዚህ ሕዝቡ ሁሉ የተነገራቸውን ቃል ተረድተው ስለ ነበረ፣ ለመብላት፣ ለመጠጣት፣ ከምግባቸው ከፍለው ለመላክና ሐሤትም ለማድረግ ሄዱ። (ነህምያ 8፥12)
የእግዚአብሔርን እውነተኛ ማንነት የሚገልጥ፣ ደግሞም እርሱን በሚያከብር ፍቅር የተሞላ ብቸኛ ደስታ፣ እውነተኛ በሆነ በእግዚአብሔር እውቀት ላይ የተመሰረተ ደስታ ነው። ታዲያማ የእኛ እውቀት አናሳና ስሕተት የተሞላ በሆነ ቁጥር፣ ደስታችንም የእግዚአብሔርን ታላቅነት በትክክል የሚገልጽ አይሆንም።
በነህምያ 8፥12 ላይ፣ እስራኤላውያን ደስ የተሰኙበት መንገድ፣ እውነተኛ የሆነውና እግዚአብሔርን የሚያከብረው ደስታ እንዴት ከልብ እንደሚመነጭ ያሳየናል። ዕዝራ የእግዚአብሔርን…
Signed Gech
5 May 2024, 05:11 UTC≈2,070 views4 reactionsread 8 August 2026 ❤️ውዶች❤️
ገና ደካሞች ሳለን
ክርስቶስ ዘመኑ ሲደርስ
ስለ ኃጢአተኞች ሞቶአልና።
ስለ ጻድቅ የሚሞት በጭንቅ ይገኛልና፤
ስለ ቸር ሰው ግን ሊሞት እንኳ የሚደፍር
ምናልባት ይገኝ ይሆናል።
ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን
ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና
እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን
የራሱን ፍቅር ያስረዳል።
ይልቁንስ እንግዲህ አሁን
በደሙ ከጸደቅን
በእርሱ ከቍጣው እንድናለን።
ጠላቶች ሳለን ከእግዚአብሔር ጋር
በልጁ ሞት ከታረቅን፥
ይልቁንም ከታረቅን በኋላ
በሕይወቱ እንድናለን፤
ይህም ብቻ አይደለም፥
ነገር ግን አሁን መታረቁን ባገኘንበት
በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል
በእግዚአብሔር ደግሞ እንመካለን።
ሮሜ 5፥6-11
እንኳን አደረሰችሁ።…
❤4
Signed Gech
18 Apr 2024, 13:35 UTC≈2,430 views7 reactionsread 8 August 2026 ስለ ኢየሱስ መማር ለምን አስፈለገ?
• እግዚአብሔር ሁሉን ነገር የፈጠረው በእርሱ በኩል ስለሆነ
• መጀመሪያውም መጨረሻውም የዘላለም አምላክ እርሱ ስለሆነ
• እግዚአብሔር የሚንጸባረቀው በእርሱ በኩል ስለሆነ
• እግዚአብሔር የሚናገረው በእርሱ በኩል ስለሆነ
• በውስጣችን የተሰወረ የእግዚአብሔር ምሥጢር ስለሆነ
• በሰማይ ያለው ብቸኛው አማላጃችን እርሱ ብቻ ስለሆነ
• እግዚአብሔር የኃጢአት ይቅርታ የሚያደርገው በእርሱ በኩል ስለሆነ
• እግዚአብሐር አብ የሚታወቀው በእርሱ በኩል ስለሆነ
• ጽድቅም ጥበብም ቅድስናም ቤዛነትም ከእግዚአብሔር ዘንድ የምናገኘው በእርሱ በኩል ስለሆነ
• እግዚአብሔር ፍቅሩን የገለጠው በእርሱ በኩል ስለሆነ
• የእግዚአብሔር አንድያ ልጅ…
👍6❤🔥1
Signed Gech
16 Mar 2024, 02:39 UTC≈3,040 viewsread 8 August 2026 ክርስቲያን ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያለው ግንኙነት ጥልቀት ከሌለው እግዚአብሔርን በሚያስክብር መንገድ ለመኖር አይችልም።
እግዚአብሔርን ለማወቅ በምናደርገው ነገር ሁሉ እርሱን በመታዘዝ ሕይወት መመላለስ ይጠበቅብናል። መንፈስ ቅዱስን እንዴት ማዳመጥ እንደሚገባን ካልተማርን በስተቀር የእግዚአብሔር ፈቃድ ምን እንደሆነ ስለማናውቅ እርሱን ደስ ለማሰኘት አንችልም። ከኃጢአት ተለይተን በቅድስና አንኖርም። ኃጢአትን ለማሸነፍ ወይም በድፍረት ለመመስከር ወይም በቤተ ክርስቲያን እንደሚገባ ለማገልገል ኃይል አናገኝም።
@THE_GRACE_0F_GOD
@THE_GRACE_0F_GOD
@THE_GRACE_0F_GOD
Signed Gech
14 Mar 2024, 04:50 UTC≈4,290 views4 reactionsread 8 August 2026 የክርስቲያን ሕይወት ተቀዳሚ ዓላማ እግዚአብሔርን ማወቅ ነው። እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ከሥላሴ አካላዊ ሕልውናዎች አንዱ ነው። ስለዚህ ልናውቀው ይገባል።
በዘመናት ሁሉ፤ ክርስቲያኖች እውነተኛው አምላክ እራሱን የገለጠው በቅድሚያ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደሆነ አጥብቀው ተናግረዋል። እውነት ምን እንደሆነ በተለይ እውነተኛው አምላክ ማን እንደሆነ የሚገልጥ የተሟላ ትክክለኛ፥ ስሕተት የሌለበት መመሪያ መጽሐፍ ቅዱስ ማለትም ብሉይ ኪዳንና አዲስ ኪዳን ነው። ክርስቲያኖች መጽሐፍ ቅዱስን በጥንቃቄ ካጠኑ በኋላ እግዚአብሔር በሦስት አካላዊ ሕልውና የተገለጠ ማለትም እግዚአብሔር አብ፥ እግዚአብሔር ወልድ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አንድ አምላክ እንደሆነ ያምናሉ።
…
❤3👍1
Signed Gech
7 Mar 2024, 03:24 UTC≈4,390 views3 reactionsread 8 August 2026 «የእግዚአብሔር ልጆች» የተወለዱት «ክሰው ዘር ከሥጋ ልማድ ወይም ከሰው ፈቃድ» አይደለም። እነርሱ የተወለዱት ከመንፈስ ነው። እነርሱ «የተወለዱት ከእግዚአብሔር» ነው። አንድ ሰው ክርስቲያን ወይም የእግዚአብሔር ቤተሰብ አባል ለመሆን ዳግም መወለድ አለበት። የእግዚአብሔር ልጆች መሆን የምንችለው በራሳችን ኀይል ወይም ፍላጎት አይደለም፤ የእግዚአብሔር ልጆች መሆን የምንችለው በእግዚአብሔር ጸጋ ብቻ ነው።
@THE_GRACE_0F_GOD
@THE_GRACE_0F_GOD
@THE_GRACE_0F_GOD
❤3
Signed Gech
5 Mar 2024, 15:47 UTC≈4,410 views4 reactionsread 8 August 2026 ኢየሱስ የመጣው «ጸጋንና እውነትን ተሞልቶ» ነው።
ጸጋ፥ እግዚአብሔር ለሰዎች የሚያሳየው ታላቅ ምሕረቱና ፍቅሩ ነው።
የእግዚአብሔር ጸጋ እጅግ ግልጽ በሆነ መንገድ የተገለጠው፣ አንድ ልጁን ኢየሱስን ለእኛ ኀጢአት ሲል እንዲሞት በላከው ጊዜ ነበር፡፡ እግዚአብሔር ለሰዎች በረከቱን የሚሰጠው በጸጋው አማካይነት ሲሆን ደኅንነትን ያገኘነውም ከእግዚአብሔር ጸጋ የተነሣ ነው። ይህም ጸጋ በክርስቶስ ተሰጠ።
@THE_GRACE_0F_GOD
@THE_GRACE_0F_GOD
@THE_GRACE_0F_GOD
❤3👍1
Signed Gech
3 Mar 2024, 15:17 UTC≈3,760 views2 reactionsread 8 August 2026 ዛሬ ዓለማችንን ብንመለከት ከብዙ ችግሮች ጋር በሚታገል ዓለም እንዳለን እንገነዘባለን። ከእነዚህ ችግሮች ጥቂቶቹ ጦርነቶች፥ ረሃብ፥ የዘር ልዩነት ውጥረትና ድህነት ናቸው። ከፍቅሩ የተነሣ የሰው ልጆች እነዚህን ችግሮች እንዲያሸንፉ የሚያስፈልጋቸውን ነገሮች ለማድረግ እግዚአብሔር ጽኑ አቋም አለው። ይህንንም በሁለት መንገዶች ያደርጋል።
👉በመጀመሪያ እግዚአብሔር በዓለም ላይ ላሉ ችግሮች ሁሉ መነሻ ለሆነው የሰው ኃጢአተኛነት መፍትሔ ለመስጠት ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን ላከው። እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ደኅንነትን ሰጥቶአል። ይህ እግዚአብሔር ለሰው ልጆች የሰጠው ተቀዳሚ ስጦታ ነው። (2ኛ. ቆሮ. 9፡15) ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ በመሞት የኃጢአትን ዋጋ …
👍2
Signed Gech
Showing the 12 most recent of 20 posts we hold for @THE_GRACE_0F_GOD. View and reaction counts are the latest single reading for each post, not a live figure, and a recent post is still accumulating both. A view count marked ≈ was rounded by Telegram before we ever saw it — t.me prints views in full below 1,000 and to three significant figures above, so ≈1,200,000 means somewhere between 1,150,000 and 1,249,999. Unmarked counts are exact. Text is reproduced from the public post preview and truncated for length.