14 Mar 2024, 17:14 UTC358 viewsread 8 August 2026 Photo
ሲኦል ማነው ?
--------------------
ሰው በኃጢያት ግዞት
ተንኮል እንደ ጢሻ ሥጋ ነፍሱን አስሮት
ላይመለስ ዳግም አንዲቷን ሞት ሲሞት
ቅጣቱ መቃጠል
በርባሮስ ውስጥ መጣል
አንደ ነዌ መንደድ ከ'ቶን እሳት መሃል ?
የለም የለም
ሲኦል ማለት እሱ አይለም
ትርጉሙን አታርቀው
ፍካሬውንም እወቀው
:
ያኔ ስቀመጥ በማህጸን
ለ'ዝች አለም ስታጭ በሰውነት ስወጠን
ደሜን ከሄዋን አጠንፍፌ
ከ አዳም አጥንት አጥንቴን ቀፍፌ
በአካል በአዕምሮ ጎልብቼ
ለመወሰነ ስብቃ ውሃን ከእሳት ለይቼ
:
ቀስ በቀስ ስፈረጥም
ስሜቴ ሲፈላ ህሊናዬ ክፋት ሲያልም
ላም ባልዋለበት ኩበት አፈሳ
የተፈጠርኩበትን አላማ ስረሳ
:
ላፍታ ምቾት ስማልል
ከመቅደሱ ጠረን ከእጣኑ ጢስ ስኮበልል
እንደ…
Signed Mickey
4 Dec 2022, 12:05 UTC498 viewsread 8 August 2026 Photo
መርገጫ እየጠፋ ፥ ደም ሞልቶት መንገዱ
መርጦ አልቃሽ ይሉናል መርጠው እራረዱ
በቅን አሳላፊ ፥ በሃገሩ ጠፍቶ
ከኋላ ቀርተናል ፥ ደም'በኛ በርክቶ
Signed Mickey
2 Jul 2021, 13:21 UTC998 viewsread 8 August 2026 Photo
#ግጠምልኝ
------------------
.
ሚካኤል እንዳለ
.
ለመልክዐ መልክሽ ፥ እጅ መንሻ ቃላት
ለውዳሴ ገላ ፥ የሚሆን የቤት ምት
ከፊደላት ፈትለህ ፥ ግጠምልኝ ላልሽው
እንግዲያስ ያውልሽ ፥ ግጥሜን ቅመሽው
- - -
የጣና ዳር እንኮይ ቁመተ ለግላጋ
የገነት ቄጤማ ፥ የጊዮን ዳር ሎጋ
የገላሽ ንጣቱ ፥ እንደ ግምጃ አለላ
ከንፈርሽ እንጆሪ ፥ የስንዴ ራስ ዛላ
እያልኩኝ ጽፊያለው
ግጠም ብለሽኛል ይህው ገጥሜያለው
- - -
እንቡጥ ጽጌሬዳ ፥ የመሰለ ጉንጭሽ
ለቀመሰው ጣፋጭ ፥ እ'ዳገዳ ጥንቅሽ
የግንቦት ሰማይ ነው ፥ የቆዳሽ ጥራቱ
የጠረንሽ ነገር ፥ አልባስጥሮስ ሽቱ
እያልኩኝ ጽፊያለው
ግጠም ብለሽኛል ይህው ገጥሜያለው
- - -
ፀጉርሽ ጢስ አባይ
የምድር መቀ…
Signed Mickey
29 Apr 2021, 17:02 UTC875 viewsread 8 August 2026 Photo
'ላምላኩ ሊታረድ ፥ በአባቱ ካራ
ይስሐቅ ሊሰዋ ፥ ሲወጣ ተራራ
አዘቅዝቆ ቢያየው
ያ እግዜር ጸፀተው
ሞቱን ላለማየት ፥ በበጉ ለወጠው
ይህው ዛሬ ደርሶ
ሰው ከበጎች አንሶ
በእግዜሩ ቦታ ፥ ተረኝነት ነግሶ
ከሰው ልጆች በላይ ግዑዛን ከበሩ እንስሶች ተለቁ
በግፈኞች ፍትህ በጎች ተቀምጠው ይሳቆች አለቁ
.
#ሚካኤል_እንዳለ
@MEBACHA
Signed Mickeý
6 Feb 2021, 13:31 UTC896 viewsread 8 August 2026 Photo
ለጉርሻ ተናንቀህ ፥ ለቅምሻ ስትለፋ
መሶቡ ተወስዶ ፥ 'ራብ እንዳይደፋህ
ወትሮም ተጋፊ ሰው ብርጭቆን ይመስላል
ቦታ እንደጠበበው ፥ አሥሬ ይጋጫል
እንግዲ ይፈታ ፥ ትርጉሙን እወቀው
ጉርሻው ዘረኝነት ፥ መሶቡም ሐገር ነው
.
#ሚካኤል_እንዳለ
.
ጉርሻ ሳይሆን መሶብ ያስረከቡህን አባቶች አስብ ፡፡
Signed Ⓜickey
3 Feb 2021, 16:27 UTC809 viewsread 8 August 2026 Photo
ማን ይብላን ?
-----------
ስለጠፋ ታማኝ ተመራጭ የሰው ዘር
ጌታ ውረድና ፥ ምርጫ ተወዳደር
እኛም በዚው ይብቃን ትለፍ ይቺ ምድር
ተብሎ ቢፈረድ ማንም አይማርም
ስልጣን ያወራቸው
እረስተዋልና ፥ መሬት ማለፏንም
ብለን
አስተምረን
እውነትን ተናግረን
'ሚሰማ ብናጣ ፥ ነፍሳችንን ይዘን
ከጅብ አፍ ለመዳን ዛፍ ብኖጣም ሸሽተን
እጅጉን የጠማው ፥ ነብር ተቀበለን
ስለዚህ ማን ይብላን ? ሆኖብናል ምርጫው
ጅብም ቢሉ ነብር ፥ መንጋጋቸው ሥል ነው
በሁለቱም ቢሆኑ ፥ ለ'ኛ ሞት አንድ ነው
#ሚካኤል_እንዳለ
Signed Ⓜickey
4 Jan 2021, 14:19 UTC783 viewsread 8 August 2026 #አትማረኝ 🙏
---------------
#ሚካኤል_እንዳለ
.
ታመው የተነሱ
እግዜርን እረሱ
የሚል ተረት አለ ፥ እሱን ያስታወሰ
ከዕለታት አንድ ቀን ፥ በኔ ላይ ደረሰ
፡፡፡፡
ለ'ለታት ሰባት ቀን ፥ ህመም ተሸክሜ
ከቤቴ ወሳንሳ ለአንድ ሱባ'ዬ የጎን ተጋድሜ
በሞትና በህይወት
በመሄድ በመምጣት
በሁለት አቅጣጫ ፥ ሥጋዬ ሲገፋ
ከቤት ስላልወጣሁ ፥ ሃጢያት 'ካይኔ ጠፋ
፡፡፡፡
ወትሮም በደካሚ
በሌለበት ቋሚ
በዛ ዝለት ጊዜ ፥ ከጓዳው ተኝቶ
እንደ ባህታዊ ፥ በሩን ደጁን ዘግቶ
ከጊዚያዊ ታዛ ፥ ከዚህ ቅዘት ዓለም
እረፍትን ፍለጋ ፥ በዐቱን ለሚያልም
ገዳም እንደመግባት
ለነፍስ እፎይታዋ ፥ ነው ለካ መታመም !!
፡፡፡፡
ታዲያ ምን ያደርጋል
ተኝቼ አልተኛሁኝ
ቀርቼ አልቀረ…
Signed Ⓜickey
25 Dec 2020, 05:44 UTC718 viewsread 8 August 2026 ያንተ ልጅ ሲበላ የኔ ልጅ ያለቅሳል
ያንተ ቤት ተከድኖ የኔ ቤት ያፈሳል
ያንተ መሬት ታርሶ የኔ ዳዋ ለብሷል
ወይ ካንተ ወይ ከኔ ያንዳችን ቀን ደርሷል
ጊዜ መሃንዲስ ነው ይሰራል ያፈርሳል
Signed Ⓜickey
27 Nov 2020, 16:41 UTC973 viewsread 8 August 2026 አንተን የሚያስንቁ ፥ 'ባይናችን ስላየን
ለስከዛሬው ሁሉ ሰይጣን ይቅር በለን
.
#ሚካኤል_እንዳለ
Signed Ⓜickey
21 Oct 2020, 16:49 UTC≈1,350 viewsread 8 August 2026 Photo
የፍጥረት ውሃ ልክ
--‐----------------
#ሚካኤል_እንዳለ
.
ከሴት ልጅ የፀዳች ፥ ዓለምን ፈጥሬ
ዠርገግ ባልኩባት ፥ ባረፍኩባት ኖሬ
የምትል ቋጠሮ
ቤት መምቻ እሮሮ
. . . አስቤ ልገጥም
ለካስ ሴት ከሌለች እናትም አትኖርም !!
የሚል መደምደሚያ ከባድ ስንኝ ቢያንቀኝ
ሰረዝኩት ሃሳቤን ወንድ የሆንኩበት ሴትነት ቢገባኝ
. . .
እናማ ካዘለች
ፈትላ ካዋሃደች
ከተሰጣት ዘንዳ
መምሰል ጽጌሬዳ
እሾህን ከጣዕም በአድ ላይ ገምዳ
ካስተባበረችው ፥ በተፈጥሮ ፀጋ
መቻል ግዴታ ነው ማሯን እስከላሱ ንቢት ስትዋጋ
. . .
በሚለው እውነታ
ቁጭ አርገው ከግርጌ 'ካውድማው ጉብታ
እንዲ ብለው ነበር ሲመክሩኝ 'የኔታ . . .
ሃላፊውን ችለህ ለመኖር ከፈለክ ዘላለም አ…
Signed Ⓜickey
14 Oct 2020, 17:15 UTC930 viewsread 8 August 2026 Photo
አፉማ የግልሽ ፥ ሰንደቋም የኔ ናት
ከንፈርሽ ይቅርብኝ ፥ ሐገሬን ልሳማት
(ሚካኤል እንዳለ)
@ethio_art
@mebacha
Signed Ⓜickey
23 Sept 2020, 15:38 UTC≈1,000 viewsread 8 August 2026 Photo
Photo, posted without a caption
Signed Ⓜickey
Showing the 12 most recent of 20 posts we hold for @Mebacha. View and reaction counts are the latest single reading for each post, not a live figure, and a recent post is still accumulating both. A view count marked ≈ was rounded by Telegram before we ever saw it — t.me prints views in full below 1,000 and to three significant figures above, so ≈1,200,000 means somewhere between 1,150,000 and 1,249,999. Unmarked counts are exact. Text is reproduced from the public post preview and truncated for length.