12 Oct 2025, 06:11 UTC≈713 viewsread 6 August 2026 ፕሮቴስታንት (Protestantism) ከ16ኛው ክፍለ ዘመን የአውሮፓ ተሐድሶ (Reformation) እንቅስቃሴ የመነጨ የክርስትና ዋነኛ ቅርንጫፍ ነው።
"ፕሮቴስታንት" የሚለው ቃል የመጣው "ተቃውሞ" ወይም "መቃወም" ከሚለው ቃል ነው። ይህ ስያሜ በዋነኝነት የተሰጠው በእንቅስቃሴው መጀመሪያ ላይ የነበሩ መሪዎች በወቅቱ በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚታዩትን ሥርዓቶች፣ ትምህርቶች እና ተግባራት በመቃወማቸው ነው።
መሠረታዊ አስተምህሮዎቹ (አምስቱ ሶላዎች):
ፕሮቴስታንትነት በአብዛኛው በአምስት ዋና ዋና መርሆዎች (ሶላዎች - Solas) ላይ የተመሠረተ ነው፦
1,መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ (Sola Scriptura):
የመጨረሻውና ብቸኛው ሥልጣን ያለው የሃይማኖ…
Signed አቤል ታደሰ ابيل
11 Apr 2025, 16:20 UTC≈1,190 viewsread 6 August 2026 Photo
በስመአበ ወወልድ ወመንፈስ ቅድስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
"ወደ ተራራው ውጡ እንጨትም አምጡ ቤቴልም ስሩ በእረሱም ደስ ይለኛል እኔም እመሰገንበታለሁ"
ይላል እግዚአብሔር ት.ሐጌ ምዕራፍ 1፥8
__
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በአዳማ ወረዳ ስር የሚገኘው ጉራጃ ፉርዳ ቅዱስ አማኑኤል ቤተክርስቲያን በእግዚአብሔር ፍቃድ የተመሰረተው በ1995 ዓ.ም ሲሆን ቤተክርስቲያኑ በወቅቱ ጥንካሬ ባለው የግንባታ እቃ ስላልተሰራ ከማርጀቱ የተነሳ ቆርቆሮው በማፍሰሱ እና ግርግዳው በመሰነጣጠቁ ምክንያት ለአገልግሎት አመቺ ባለመሆኑ እስካሁን ድረስ የቃልኪዳን ታቦቱ በመቃኞ ቤት ውስጥ ይገኛል።ቤተክርስቲያኒቱ በገጠራማ አካበቢ ላይ ስላለች ብዙም ምዕመናን ስለሚያገኝበ…
Signed አቤል ታደሰ ابيل
11 Apr 2025, 16:20 UTC≈1,250 viewsread 6 August 2026 የቻላቹትን ከበረከቱ ተሳተፉ screenshot lakuleng::አሐው!
Signed አቤል ታደሰ ابيل
6 Apr 2025, 10:05 UTC≈708 viewsread 6 August 2026 የሌሊቱ ተማሪ ኒቆዲሞስ
ኒቆዲሞስ ፈሪሳዊ፥ ከአይሁድ አለቆችና መምህራና አንዱ ነው። በዮሐ. 3÷1 ከፈሪሳውያን ወገን የአይሁድ አለቃ የሆነ ኒቆዲሞስ የተባለ አንድ ሰው እንደነበረና እርሱም በሌሊት ወደ ጌታችን መጥቶ እንደተማረ ተጠቅሷል። (ዮሐ 1÷2) በአይሁድ አለቆች ፊትም ”ሕጋችን አስቀድሞ ሳይሰማ የሠራውንም ሳያውቅ በሰው ይፈርዳልን?” በማለት ስለ መድኃኔዓለም ክርስቶስ የተናገረ እሱ ነው ኒቆዲሞስ “መምህር ሆይ ልታስተምር ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደመጣህ እናውቃለን እግዚአብሔር ከርሱ ጋር ከሆነ በቀር አንተ የምታደርገውን ይህን ተአምር ሊያደርገ የሚችል የለምና።" በማለት ተናገረ።(ዮሐ3፥2) በዚህ ጊዜ ጌታችን የገነት በር ስለሆነው ስለ ምስጢረ ጥምቀት …
Signed አቤል ታደሰ ابيل
9 Mar 2025, 08:23 UTC≈1,120 viewsread 6 August 2026 ምኵራብ
የቤተ ክርስቲያን እንዚራ ቅዱስ ያሬድ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ወደ ምኵራብ መግባት አይቶ በወንጌል የተጻፈውን ተርጒሞ ሳምንቱን በዜማ ያንን ቤተ መቅደስ የገባበትንና ቤተ መቅደሱ ውስጥ ይሸጡ ይነግዱ የነበሩ ወንበዴዎችን ያባረረበት ቅጽበት አንሥቶ ለጾሙ ሳምንት ምኵራብ ብሎ አርእስት ሰጥቶታል።
ምኵራብ “ቤተ አዳራሽ፣ ኮረብታ፣ ተራራ የሚያህል ታላቅ ሕንጻ፣ ሰቀላ መሰል አዳራሽ” ማለት ሲሆን ናቡከደነጾር ኢየሩሳሌምን ወርሮ ቤተ መቅደሱን ባፈረሰበት ሰዓት እና ሕዝቡንም በምርኮ ወደ ባቢሎን በአግአዘ (በአፈለሰ) ወቅት በምርኮ ሀገር ሆነው እግዚአብሔርን የሚያመልኩበት፣ ለጸሎት እና መሥዋዕት ማሳረጊያ ይሆናቸው ዘንድ ባገኙት ቦታ ድንኳን …
Signed አቤል ታደሰ ابيل
29 Nov 2024, 04:47 UTC≈1,070 viewsread 6 August 2026 ነገሮችን ለማስተካከል እግዚአብሔር ስንት ሰው ይበቃዋል?
.
ቤተ ክህነታችንን ለማስተካከል እግዚአብሔር ስንት ሰው ይበቃዋል?
.
የቤተ ክርስቲያናችንን ችግሮች ለመቅረፍና ለማሻሻል እግዚአብሔር ስንት ሰው ይበቃዋል?
.
የምንፈልገውን አይነት የኦርቶዶክሳዊ አገልግሎት ዐውድ ለመፍጠር እግዚአብሔር ስንት ሰው ይበቃዋል?
.
ሊሠራ ከወደደ እግዚአብሔር በጥቂት ሰዎችም ይሠራል፤ ይሆን ዘንድ ከፈቀደም አንድ ሰው ይበቃዋል!!! የግብጽ ቤተ ክርስቲያን ያበበችው ሐቢብ ጊዮርጊስ በሚባል አንድ ዲያቆን እኮ ነው!!!
.
እግዚአብሔር በጥቂት ሰዎችም ሊሠራ ቢወድ እኛ ከእነዚያ ጥቂት ሰዎች መካከል ለመሆን ዝግጁዎችና ፈቃደኞች እንሆን ይሆንን?
.
እግዚአብሔር በአንድ ሰው ሊሠራ ፈ…
Signed አቤል ታደሰ ابيل
14 Nov 2024, 17:13 UTC≈954 viewsread 6 August 2026 " የመንፈሳዊነት ግቡ፤ የአገልጋይነት ልኩ፤ የክርስትናችንም ጥጉ ወደ እግዚአብሔር መድረስ፣ እግዚአብሔርን ማግኘትና ከእግዚአብሔር ጋር መሆን ነው! "
.
“እናንተ በመጽሐፍት የዘለዓለም ሕይወት እንዳላችኹ ይመስላችኋልና፥ እነርሱን ትመረምራላችኹ፤ እነርሱም ስለ እኔ የሚመሰክሩ ናቸው፤ ነገር ግን፥ ሕይወት እንዲኾንላችኹ ወደ እኔ ልትመጡ አትወዱም።” ዮሐ 5፤39-40
.
የመንፈሳዊነት ግቡ፤ የአገልጋይነት ልኩ፤ የክርስትናችንም ጥጉ ወደ እግዚአብሔር መድረስ፣ እግዚአብሔርን ማግኘትና ከእግዚአብሔር ጋር መሆን ነው!!!
.
ክርስቲያኖች የሆንነው እግዚአብሔርን ለማግኘትና ከእግዚአብሔር ጋር ለመሆን ነው!
.
መጽሐፍ ቅዱስ የምናነበውና ቅዱሳት መጽሐፍትን የምንመረምረው እ…
Signed አቤል ታደሰ ابيل
14 Nov 2024, 10:29 UTC≈741 viewsread 6 August 2026 ✝✝✝ጳጳሳት ደመወዝተኞች፤ ካህናትስ ለምን ፈሪዎች ሆኑ?
.
#ጳጳሳት በደመወዝ ማደራቸው ተገቢ አለመሆኑ ተደጋግሞ ይነሳል! ስማቸውንም ገንዘብ ነክ ከሆኑ ጉዳዮች ጋር እያነሳን አብዝተን እንነቅፋቸዋለን! . . . ደመወዛቸው ቢቀር ስንል ግን እንዴት እንደሚያድሩና ሊያገለግሉን ሲወጡና ሲወርዱ ወጪዎቻቸውና አስፈላጊ ግብአቶች እንዴት ሊሟሉላቸው እንደሚችሉ አማራጭ አላስቀመጥንም!
.
ለመሆኑ ስለጳጳሳቶቻችን ምን ያህል እናውቃለን? የምናውቀውስ ምን ያህል በቂ ነው? በምናውቀውስ ምን ያህል እርግጠኞች ነን? . . . ብዙዎቹ የቤተ ክርስቲያናችን ጳጳሳት (Exceptions are there) ረጅሙን ጊዜያቸውን በትምህርት ያሳለፉ፤ ሙሉ እነርሱነታቸውን ለቤተ ክርስቲያን…
Signed አቤል ታደሰ ابيل
10 Sept 2024, 17:57 UTC≈822 viewsread 6 August 2026 Forwarded from @behlateabewPhoto
"የጽድቅን ሥራ የምንሠራበት ከኾነ አዲሱ ቀን ብቻ ሳይኾን አዲሱ ዓመት ለእኛ መልካም ነው፡፡ ኀጢአት የምንሠራበት ከኾነ ግን ቀኑ ብቻ ሳይኾን አዲሱ ዓመትም ክፉና መከራ የመላበት ይኾንብናል፡፡ አዲሱን ዓመት በበጐ ሥራ የምንጀምረው ከኾነ በዓመቱ በምናደርገው ማንኛውም ክንውን ላይ በጐ ተጽዕኖ ያሳድርብናል፡፡"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
መልካም አዲስ ዓመት🙏
Signed አቤል ታደሰ ابيل
22 Aug 2024, 08:54 UTC≈859 viewsread 6 August 2026 የእመቤታችን በዓለ ዕርገት
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ያረገችበት ዕለት ነሐሴ ዐሥራ ስድስት ቀን በቤተ ክርስቲያናችን ይከበራል፡፡
ሐዋርያት ከእመቤታችን ድንግል ማርያም ዕረፍት በኋላ ከእነርሱ በመለየቷ ባዘኑበት ወቅት የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጠላቸው፤ እርሷን በሥጋ ያዩ ዘንድም ተስፋ ሰጣቸው፡፡
በዚያን ጊዜ ወንጌላዊ ዮሐንስ እስያ በሚባል አገር እያስተማረ በነበረበት በነሐሴ ወር ዐሥራ ስድስተኛ ቀን ተድላ ደስታ ወደ አለባት ገነት በመንፈስ ቅዱስ ተነጠቀ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስንም የእመቤታችን ማርያም ሥጋዋ ካለበት ከዕፀ ሕይወት ዘንድ ተቀምጦ አየው፡፡
የንጽሕት እናቱንም ሥጋ ታወጣ ዘንድ ምድርን እንዲጠሩዋት ሰባቱን የመ…
Signed አቤል ታደሰ ابيل
22 Aug 2024, 08:54 UTC≈578 viewsread 6 August 2026 Photo
Photo, posted without a caption
Signed አቤል ታደሰ ابيل
22 Aug 2024, 08:54 UTC≈742 viewsread 6 August 2026 በኪሩቤል ሠረገላ ተቀምጣ ከዐረገች በኋላም በልጆችዋና በፈጣሪዋ ቀኝ በታላቅ ክብር ተቀመጠች፡፡ በዚህን ጊዜ ወንጌላዊ ዮሐንስ ከእርሷ በረከትን ተቀብሎ ከሰገደላት በኋላ ተመልሶ ወደ ምድር ወረደ፤ ሐዋርያትንም ተሰብስበው ስለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋ ፈጽሞ ሲያዝኑና ሲተክዙ አገኛቸው፡፡ እርሱም እንዳየ፣ እንደሰማና ሥጋዋንም በታላቅ ክብር በምስጋና እንዳሳረጓት ነገራቸው፡፡
ሐዋርያትም ይህን በሰሙ ጊዜ ዮሐንስ እንዳየና እንደሰማ ባለማየታቸውና ባለመስማታቸው እጅግ አዘኑ፡፡ ከዚያም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጦ ‹‹የፍቅር የአንድነት ልጆች፤ ሰላም ይሁንላችሁ! ስለ እናቴ ማርያም ሥጋ ለምን ታዝናላችሁ፡፡ እነሆ እኔ እርስዋን በሥጋ ላሳያችሁ፤ ልባች…
Signed አቤል ታደሰ ابيل
Showing the 12 most recent of 18 posts we hold for @hamreel. View and reaction counts are the latest single reading for each post, not a live figure, and a recent post is still accumulating both. A view count marked ≈ was rounded by Telegram before we ever saw it — t.me prints views in full below 1,000 and to three significant figures above, so ≈1,200,000 means somewhere between 1,150,000 and 1,249,999. Unmarked counts are exact. Text is reproduced from the public post preview and truncated for length.